የአፍሪካ ሉዓላዊ ምርጫ - ሞስኮ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና በጊኒ የተካሄደውን ሰላማዊ ምርጫ በደስታ ትቀበላለች ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
15:15 30.12.2025 (የተሻሻለ: 15:24 30.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሉዓላዊ ምርጫ - ሞስኮ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና በጊኒ የተካሄደውን ሰላማዊ ምርጫ በደስታ ትቀበላለች ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እሁድ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊና የፓርላማ አጠቃላይ ምርጫ እንዲሁም በጊኒ ሪፐብሊክ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በደስታ እንደሚቀበል አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ እንዳመለከተው፣ እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ገለጻ፣ ምርጫው በሰላም የተካሄደ ሲሆን ምንም ዓይነት ከባድ ጥሰቶች አልተስተዋሉም።
ሞስኮ፣ ምርጫዎቹን ሁለቱ ሀገራት በዓለም አቀፍ ህግ አንኳር መርሆች ላይ የተመሰረተ፣ ሉዓላዊ የእድገት ጎዳናን ለመከተል ያላቸው ቁርጠኝነት ግልጽ ማሳያ እንደሆነ ትመለከታለች ሲል አጽንኦት ሰጥቷል።
ሚኒስቴሩ በተጨማሪም ለማዕከላዊ አፍሪካ እና ለጊኒ ሕዝቦች ቀጣይ የዴሞክራሲ እድገት እና ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን የማስቀጠል መልካም ምኞቱን ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X