ሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ
ሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.12.2025
ሰብስክራይብ

ሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ

ሩዋንዳ ከአፍሪካ ሕብረት እና ከምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጎን በመሰለፍ ለሶማሊያ ያላትን ድጋፍ የገለጸች ሲሆን፤ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት በጋራ ሰላም እና ብልጽግና ላይ የተመሰረተ የቀጣይ ጉዞ እንዲኖር ማበረታቷን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ እስራኤል ለሶማሊላንድን እንደ ነፃ ሀገር እውቅና መስጠቷን በተመለከተ ያላትን ስጋት ገልጻለች። ይህ ድርጊት የሶማሊያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሚጥስ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ሰላም አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን አስታውቃለች።

ደቡብ አፍሪካ "አንድ ሀገር ነፃነቷን ስታገኝ የነበራትን ድንበር ይዛ ትቀጥላለች የሚለውን" የአፍሪካ ሕብረት መርህ በድጋሚ በማረጋገጥ፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የውጭ ጣልቃ ገብነትን ውድቅ እንዲያደርግ እና አንዲት የጸናች እና የተረጋጋች ሶማሊያን እንዲደግፍ አሳስባለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ
ሩዋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ ለሶማሊያ የግዛት አንድነት ያላቸውን ድጋፍ ዳግም አረጋገጡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.12.2025
አዳዲስ ዜናዎች
0