https://amh.sputniknews.africa
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ“ይህ በዩክሬን ልሂቃንና በአውሮፓ ደጋፊዎቻቸው የተደረገ ሌላ ጥረት ነው፡፡ ይህም ግጭቱን ከመቀጠል አልፎ... 30.12.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-12-30T11:48+0300
2025-12-30T11:48+0300
2025-12-30T12:34+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/0c/1e/2718147_0:42:800:492_1920x0_80_0_0_f53af86e248c7fb187da679e2408a895.jpg
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ“ይህ በዩክሬን ልሂቃንና በአውሮፓ ደጋፊዎቻቸው የተደረገ ሌላ ጥረት ነው፡፡ ይህም ግጭቱን ከመቀጠል አልፎ ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግ ነው። እኛ አሁን የምንነጋገረው አንድን ታላቅ መሪ ለመግደል ስለተደረገ ሙከራ ነው፤ ይህም እንደ ኖርድ ስትሪም ጥቃት ካሉ ሌሎች መገለጫዎች ልቆ የሚታይ ታላቅ ማባባሻ ነው።” ሲሉ የኩባው ራውል ሮአ ጋርሺያ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተቋም ፕሮፌሰር የኦስማኒ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡ በእሳቸው አስተያየት፣ በፑቲን ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያ ላይ የተሰነዘረው ይህ ጥቃት ጠብ አጫሪነት ነው። ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች በሙሉ ሩሲያ አውሮፓን ለማጥፋትና ከድንበሯ በላይ ለመስፋፋት የምትፈልግ አጥቂ አገር እንደሆነች አድርጎ ለመውቀስ የሚያገለግል ተደጋጋሚ ስትራቴጂ አካል ነው ሲሉም አክለዋል።“ይህ ጥቃት የተከሰተው ግጭቱን ለመፍታት በሞስኮ እና በአሜሪካ መካከል ድርድር በሚደረግበት ወቅት ነው። ይህ ደግሞ ለኪዬቭ አገዛዝም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ ላሉ አጋሮች አይመችም፡፡ ምክንያቱም ዩክሬንን ለመርዳትና ሩሲያን ለማጥፋት ያላቸው ንግግርና ፕሮጀክት ፍጹም ውድቀት ይሆናል።”የዚህ የሽብር ድርጊት አለመሳካት የሞስኮን አቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ የበለጠ ያጠናክራል፤ በተጨማሪም “ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል” ሲሉ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ደምድመዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2025
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/0c/1e/2718147_45:0:756:533_1920x0_80_0_0_14c8d1d38bf4863c4bdcb3452ce20012.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ
11:48 30.12.2025 (የተሻሻለ: 12:34 30.12.2025) በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ
“ይህ በዩክሬን ልሂቃንና በአውሮፓ ደጋፊዎቻቸው የተደረገ ሌላ ጥረት ነው፡፡ ይህም ግጭቱን ከመቀጠል አልፎ ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግ ነው። እኛ አሁን የምንነጋገረው አንድን ታላቅ መሪ ለመግደል ስለተደረገ ሙከራ ነው፤ ይህም እንደ ኖርድ ስትሪም ጥቃት ካሉ ሌሎች መገለጫዎች ልቆ የሚታይ ታላቅ ማባባሻ ነው።” ሲሉ የኩባው ራውል ሮአ ጋርሺያ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተቋም ፕሮፌሰር የኦስማኒ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡
በእሳቸው አስተያየት፣ በፑቲን ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያ ላይ የተሰነዘረው ይህ ጥቃት ጠብ አጫሪነት ነው። ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች በሙሉ ሩሲያ አውሮፓን ለማጥፋትና ከድንበሯ በላይ ለመስፋፋት የምትፈልግ አጥቂ አገር እንደሆነች አድርጎ ለመውቀስ የሚያገለግል ተደጋጋሚ ስትራቴጂ አካል ነው ሲሉም አክለዋል።
“ይህ ጥቃት የተከሰተው ግጭቱን ለመፍታት በሞስኮ እና በአሜሪካ መካከል ድርድር በሚደረግበት ወቅት ነው። ይህ ደግሞ ለኪዬቭ አገዛዝም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ ላሉ አጋሮች አይመችም፡፡ ምክንያቱም ዩክሬንን ለመርዳትና ሩሲያን ለማጥፋት ያላቸው ንግግርና ፕሮጀክት ፍጹም ውድቀት ይሆናል።”
የዚህ የሽብር ድርጊት አለመሳካት የሞስኮን አቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ የበለጠ ያጠናክራል፤ በተጨማሪም “ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል” ሲሉ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ደምድመዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X