በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ
በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.12.2025
ሰብስክራይብ

በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ ኪዬቭ የሰነዘረችው ጥቃት ‘ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል’ ሲሉ ባለሙያ ተናገሩ

“ይህ በዩክሬን ልሂቃንና በአውሮፓ ደጋፊዎቻቸው የተደረገ ሌላ ጥረት ነው፡፡ ይህም ግጭቱን ከመቀጠል አልፎ ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግ ነው። እኛ አሁን የምንነጋገረው አንድን ታላቅ መሪ ለመግደል ስለተደረገ ሙከራ ነው፤ ይህም እንደ ኖርድ ስትሪም ጥቃት ካሉ ሌሎች መገለጫዎች ልቆ የሚታይ ታላቅ ማባባሻ ነው።” ሲሉ የኩባው ራውል ሮአ ጋርሺያ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተቋም ፕሮፌሰር የኦስማኒ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡

በእሳቸው አስተያየት፣ በፑቲን ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያ ላይ የተሰነዘረው ይህ ጥቃት ጠብ አጫሪነት ነው። ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች በሙሉ ሩሲያ አውሮፓን ለማጥፋትና ከድንበሯ በላይ ለመስፋፋት የምትፈልግ አጥቂ አገር እንደሆነች አድርጎ ለመውቀስ የሚያገለግል ተደጋጋሚ ስትራቴጂ አካል ነው ሲሉም አክለዋል።

“ይህ ጥቃት የተከሰተው ግጭቱን ለመፍታት በሞስኮ እና በአሜሪካ መካከል ድርድር በሚደረግበት ወቅት ነው። ይህ ደግሞ ለኪዬቭ አገዛዝም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ ላሉ አጋሮች አይመችም፡፡ ምክንያቱም ዩክሬንን ለመርዳትና ሩሲያን ለማጥፋት ያላቸው ንግግርና ፕሮጀክት ፍጹም ውድቀት ይሆናል።”

የዚህ የሽብር ድርጊት አለመሳካት የሞስኮን አቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ የበለጠ ያጠናክራል፤ በተጨማሪም “ዩክሬን በቀጥታ በጦር ሜዳ የማሸነፍ አቅም እንደሌላት ያሳያል” ሲሉ ፈርናንዴዝ ፓቼኮ ደምድመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0