በፑቲን መኖሪያ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት የዩክሬን የሰላም ስምምነትን ለማደናቀፍ በሚፈልጉ ኃይሎች የታቀደ ነው - ወታደራዊ ተንታኝ

በፑቲን መኖሪያ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት የዩክሬን የሰላም ስምምነትን ለማደናቀፍ በሚፈልጉ ኃይሎች የታቀደ ነው - ወታደራዊ ተንታኝ
“እነርሱ ወደ ኋላ ማፈግፈግንና በድንበር አካባቢያችን ያለው ሁኔታ እንዲረጋጋ መፍቀድን እንደ አማራጭ አይመለከቱትም። ስለዚህ፣ የድርድር ሂደቱን ለማደናቀፍ ተከታታይ ሙከራዎችን እያደረጉ ነው” ሲሉ ወታደራዊ ተንታኝ አሌክሳንደር ስቴፓኖቭ እሁድ ምሽት በኖቭጎሮድ ግዛት በሚገኘው የፑቲን መኖሪያ ላይ በ91 ድሮኖች የተሰነዘረውን ጥቃት አስመልክቶ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
🟠 “ይህንን አቋም ቁልፍ የሆኑ የአውሮፓ ሕብረት መሪዎች በግልጽ በሚያንጸባርቁት አመለካከት አይተነዋል። አሁን ደግሞ በመረጃ ድርጅቶች በተለይም የብሪታንያ ተቋም እቅዶች ውስጥ እያየነው ነው፤ እነዚህ አካላት በስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባላቸው ኢላማዎች ላይ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም፣ እንዲሁም በከፍተኛ የሩሲያ ወታደራዊ መኮንኖች ላይ ያነጣጠረ የግድያ ሙከራ ለማድረግ ማቀዳቸውን ቀጥለዋል። ይህም ጦርነቱን የመንግስት ሽብርተኝነት መሣሪያዎችን በመጠቀም ወደ ዘላቂ የውክልና-ውህድ ጦርነት እየቀየረው ነው፡፡”
🟠 ስቴፓኖቭ አክለውም፣ እነዚህ ጥረቶች የኪዬቭን አገዛዝ የበለጠ “ሕገ-ወጥ” ለማድረግ ያገለግላሉ ብለዋል። ጥቃቶቹ የዩክሬን ባለስልጣናት “የጦር ወንጀለኞች እና በይበልጥ ደግሞ ዓለም አቀፍ አሸባሪዎች መሆናቸውን፣ በዚህም ግዛት የማስተዳደርም ሆነ የዜጎችን ህይወት የመቆጣጠር መብት እንደሌላቸው” ግልጽ ያደርጋሉ ብለዋል።
🟠 ተንታኙ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት፣ ከእንዲህ አይነት አካላት ጋር መደራደር “የማይቻል ነው፤ እንዲሁም ማንኛውንም የዓለም አቀፍ ግንኙነት ደንብ አይመጥኑም”።
🟠 ስቴፓኖቭ ከእሁዱ ጥቃት በኋላ፣ የአሰሳ እና የዒላማ መቆጣጠሪያ ስርዓቶችን ጨምሮ በአሜሪካ እና በዩክሬን መካከል ያለው ወታደራዊ-ቴክኒካዊ እና የመረጃ ትብብር “በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል” ብለው ይጠብቃሉ።
🟠 ስቴፓኖቭ ሲቀጥሉም “የአሜሪካ መግለጫዎች በእውነተኛ ፍላጎት የታጀቡ ከሆኑ፣ በምዕራባውያን በኩል የቀረቡትን የአሜሪካንን ጨምሮ የሁሉንም የጦር መሣሪያዎች የመቆጣጠሪያ ስርዓቶች ከርቀት ማሰናከል ይቻላል። እንዲሁም በተወሰኑ ደረጃዎች ውስብስብ የሆኑትን "የፓትሪዮት" የአየር መከላከያ እና "ኤችአይኤምኤአርኤስ" የረጅም ርቀት ስርዓቶችን የሚያንቀሳቅሱ የአሜሪካ ወታደራዊ ባለሙያዎች እንዳይገኙ ማድረግ ይቻላል” ብለዋል።
🟠 ተመሳሳይ ሁኔታ ለስታርሊንክ ኢንተርኔት አገልግሎትም የሚሰራ ሲሆን፣ አገልግሎቱ ቢቋረጥ የዩክሬን ጦርን “በጥቂት ሰዓታት ውስጥ” መሄጃውን የማያውቅ ሊያደርገው እንደሚችል ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |