'ሰላምን አይፈልጉም'- ኪዬቭ በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሰነዘረችው ጥቃት "ታላቅ ግድያ" የመፈጸም ሙከራ ነው ሲሉ ባለሙያ ገለጹ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ'ሰላምን አይፈልጉም'- ኪዬቭ በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሰነዘረችው ጥቃት "ታላቅ ግድያ" የመፈጸም ሙከራ ነው ሲሉ ባለሙያ ገለጹ
'ሰላምን አይፈልጉም'- ኪዬቭ በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሰነዘረችው ጥቃት ታላቅ ግድያ የመፈጸም ሙከራ ነው ሲሉ ባለሙያ ገለጹ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.12.2025
ሰብስክራይብ

'ሰላምን አይፈልጉም'- ኪዬቭ በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሰነዘረችው ጥቃት "ታላቅ ግድያ"  የመፈጸም ሙከራ ነው ሲሉ ባለሙያ ገለጹ

"ይህ ክስተት የሚያሳየው፣ ሰላምን የማይፈልግና ይህንን ግጭት በማንኛውም ዋጋ ለማባባስና ለማስቀጠል የቆረጠ አካል ጋር እየተገናኘን መሆናችንን ነው። እየተነጋገርን ያለነው በኖቭጎሮድ ግዛት በሚገኘው የፑቲን የግል መኖሪያ ላይ ስለተሰነዘረው ጥቃት እንጂ ስለ ክሬምሊን ወይም ስለ ሞስኮ አካባቢ አይደለም። እኛ በቀጥታ 'ታላቅ ግድያ' (በከፍተኛ ፖለቲከኛ ላይ የሚፈጸም) የመፈጸም ሙከራ ገጥሞናል" ሲሉ ዓለም አቀፍ ተንታኝ ታዲዮ ካስተሊዮኔ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

እንደ ተንታኙ ማብራሪያ፣ ይህ ጥቃት የተፈጸመው ወደ ድርድር የሚያመሩ ጥሩ ሁኔታዎች በታዩበት ወቅት ሲሆን፣ ይህም የውይይት ጠረጴዛው አሁንም እየተስተጓጎለና እየተገፋ መሆኑን ያሳያል።

እንደ ተንታኙ ገለጻ፣ ዩክሬን የምዕራባውያን የመረጃ ድጋፍ ከሌላት እንዲህ አይነት ጥቃት የመፈጸም አቅም አይኖራትም። ካስተሊዮኔ ሞስኮ በተደጋጋሚ እንደምትገልጸው ሁሉ፣ እንግሊዝም ለኪዬቭ ዋነኛ የወታደራዊ መረጃ ምንጭ መሆኗን በዋነኝነት ጠቁመዋል።

"ዶናልድ ትራምፕ ከፑቲን ጋር እየተደራደሩ ቢሆን ኖሮ፣ የዚህን ያህል መጠን ያለው ጥቃት ሪፖርት ሊደርሳቸው ይገባ ነበር፤ እርሳቸውም ጥቃቱ እንዲፈጸም አይፈቅዱም ነበር" ሲሉም አክለዋል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0