#viral | የሱዳን ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ በአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ ላይ ራሱን ስቶ ሜዳ ላይ ወደቀ
20:55 29.12.2025 (የተሻሻለ: 21:04 29.12.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
#viral | የሱዳን ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ በአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ ላይ ራሱን ስቶ ሜዳ ላይ ወደቀ
ክስተቱ የተፈጠረው በምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ከኢኳቶሪያል ጊኒ ጋር እየተጫወቱ ባሉበት የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ ሲሆን፣ ሞንገድ አቡዛይድ በድንገት በራሱ የግብ ክልል አቅራቢያ ላይ ወድቋል።
ጨዋታው ወዲያውኑ የተቋረጠ ሲሆን፣ የሕክምና ቡድን ለ10 ደቂቃ ያህል ሜዳ ውስጥ እርዳታ አድርጎለታል።
ተጫዋቹ በኋላ ወደ ሜዳ ተመልሶ ጨዋታውን የቀጠለ ሲሆን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ለአጭር ጋዜ ንቃተ ሕሊናውን ያጣበት ምክንያት ከደም ግፊት ወይም ከደም ስኳር መጠን ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል።
ሱዳን ጨዋታውን 1 ለ 0 በማሸነፍ በሞሮኮ እየተካሄደ ባለው ውድድር የመጀመሪያዎቹን 3 ነጥቦች አግኝታለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X