ሱዳን በኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ውስጥ ብትሆንም የወርቅ ምርቷ ካለፉት 5 ዓመት የዘንድሮ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል የመንግሥት ኩባንያ አስታወቀ

ሱዳን በኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ውስጥ ብትሆንም የወርቅ ምርቷ ካለፉት 5 ዓመት የዘንድሮ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል የመንግሥት ኩባንያ አስታወቀ
የሀገሪቱ የወርቅ ምርት በዚህ ዓመት 70 ቶን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ዓመታዊ ግቡን በ113 በመቶ አልፏል ሲል የሀገሪቱ የማዕድን ሚኒስቴር የቁጥጥር አካል የሆነው የሱዳን ማዕድን ሃብት ኩባንያ አስታውቋል።
ይህ ከፍተኛ ጭማሪ ለአገር ውስጥ ኢኮኖሚ ወሳኝ የሆነ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ ከ426 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አስገኝቷል ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ አክሎም የቀጠሉ ብሔራዊ ፈተናዎች ውስጥም ቢሆን የማዕድን ዘርፉ ያሳየውን ጠንካራ መቋቋም አድንቋል።
የወርቅ ምርት መጨመር የውጭ ምንዛሪ ዋነኛ ምንጭ ሆኗል፤ የምርቱ ጭማሪ የተገኘው ባለፉት ጊዜያት የነበሩትን የወጪ ንግድ መሰናክሎች በመፍታት እና ከአምራቾች ጋር የበለጠ ተለዋዋጭ ፖሊሲዎችን በመከተል እንደሆነ ተገልጿል።
ባለሥልጣናት የወደፊት ትኩረታቸው በዲጂታላይዜሽን፣ በጠንካራ ደንብ እና ትላልቅ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ላይ ይሆናል ሲል የመንግሥት ኩባንያው ገልጿል።
ከጠቅላላው ምርት ከ85 በመቶ በላይ ለሚያዋጡት ባህላዊ ወርቅ አውጪዎች የሚሠጥ ድጋፍ ላይ አጽንዖት ተሰጥቷል፤ ይህም የሚደረገው የኮንትሮባንድ ንግድን ለመቀነስ እና ኢኮኖሚያዊ ገቢን ከፍ ለማድረግ የጉምሩክ አሰራሮችን በማቃለል ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X