በአዲስ አበባ 32 አዳዲስ የፖሊስ እና የእሳትና አደጋ ሥጋት መከላከያ ተቋማት ተመረቁ
20:03 29.12.2025 (የተሻሻለ: 20:14 29.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ 32 አዳዲስ የፖሊስ እና የእሳትና አደጋ ሥጋት መከላከያ ተቋማት ተመረቁ
ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የተበሰረበት ዕለት ነው፤ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል፡፡
"እነዚህ ተቋማት በየአካባቢው መገንባታቸው ወንጀልን ለመከላከልና ድንገተኛ አደጋዎች በሚያጋጥሙበት ወቅት የሚሰጠውን የምላሽ ጊዜ በእጅጉ በማሳጠር፣ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለመቀነስ ትልቅ አቅም ይፈጥራሉ" ብለዋል፡፡
ከንቲባዋ ቴክኖሎጂን በሚጠቀሙ አካታች መሠረተ ልማቶች የተደራጁ ናቸው ያሏቸው ተቋማቱ፦
የፖሊስ መምሪያዎችን፣
ጣቢያዎች፣
ካምፖች እና
የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከያዎችን አካትተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X





