በፑቲን እና በትራምፕ መካከል የተደረገው አዲስ የስልክ ውይይት በአዎንታዊ መልኩ መጠናቀቁን ዋይት ሐውስ አስታወቀ
19:04 29.12.2025 (የተሻሻለ: 19:54 29.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በፑቲን እና በትራምፕ መካከል የተደረገው አዲስ የስልክ ውይይት በአዎንታዊ መልኩ መጠናቀቁን ዋይት ሐውስ አስታወቀ
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ የሚከተሉት ቁልፍ ዝርዝር ሐሳቦች በውይይቱ መነሳታቸውን ገልፀዋል፦
▪ ትራምፕ በዩክሬን ጦር ኃይሎች በፑቲን መኖሪያ ላይ ባደረጉት የጥቃት ሙከራ መደንገጣቸውንና መቆጣታቸውን ገልጸዋል። ጥቃቱ አሜሪካ ከለለንስኪ ጋር የምፀራበትን አካሄድ ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድርም አክለዋል።
▪ትራምፕ፣ ኪዬቭ የአንዳፍታ የተኩስ አቁም ከመፈለግ ይልቅ ሁሉን አቀፍ ስምምነት ለማሳካት እንድታተኩር መክረዋል።
▪ ሩሲያ የዩክሬን የውሳኔ ሐሳቦችን ለትርጉም የተጋለጡ አድርጋ ትመለከታቸዋለች፤ ይህም ዩክሬን ከምትገባው ቃል እንድታመልጥ የሚያስችላት ነው።
▪ ሩሲያ ከአሜሪካ ጋር በዩክሬን ጉዳይ ቀደም ሲል የተደረሱባቸውን በርካታ ስምምነቶችና ውሳኔዎች በተመለከተ አቋሟን ትገመግማለች።
▪ ትራምፕ በዘለንስኪ ቡድን የተገኙ አንዳንድ ውጤቶችን ለፑቲን አሳውቀዋቸዋል።
▪ ፑቲን ሩሲያ ሰላምን ለመፈለግ ከአሜሪካና ጋር በቅርበትና ፍሬያማ በሆነ መንገድ ለመሥራት እንደምትፈልግ አጽንዖት ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X