ማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የሞስኮ "የቅርብ ወዳጆች" ናቸው - በማሊ የሩሲያ አምባሳደር

ሰብስክራይብ

ማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የሞስኮ "የቅርብ ወዳጆች" ናቸው - በማሊ የሩሲያ አምባሳደር

​እ.ኤ.አ. በ2025 የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምገም በባማኮ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ኢጎር ግሮሚኮ ለስፑትኒክ አፍሪካ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ፣ ሩሲያ እና የሳሕል ሀገራት ጥምረት በትብብራቸው እድገት መሰረት በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 በርካታ ዝግጅቶችን እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል።

​“ሦስቱ የሳሕል ሀገራት ጥምረት አባላት ሩሲያ የወዳጅነት እና ቅን ግንኙነት የመሠረተችባቸው ሀገራት ናቸው። የወንድማማችነት ትስስር ያለን ሲሆን በዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተለይም በተመድ ውስጥ አብረን እንሰራለን” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

​ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጹት ዲፕሎማቱ፣ ሩሲያ ከሁለት ዓመት በፊት በቡርኪና ፋሶ ኤምባሲ መክፈቷን እና በቅርቡ ደግሞ በኒጀር ኤምባሲ ማስመረቋንና አዲሱ የኒጀር አምባሳደርም የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸውን ጠቁመዋል።

​“ከማሊ ወዳጆቻችን ጋር ያለን ግንኙነት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሰብአዊ እርዳታ እና በስፖርት ዘርፎች ማደጉን ይቀጥላል” ሲሉ አመልክተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0