አልጄሪያ ለመላው የድህረ-ቅኝ ግዛት ዓለም የሕግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች - የሩሲያ ፓርላማ የታሕታይ ምክር ቤት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአልጄሪያ ለመላው የድህረ-ቅኝ ግዛት ዓለም የሕግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች - የሩሲያ ፓርላማ የታሕታይ ምክር ቤት
አልጄሪያ ለመላው የድህረ-ቅኝ ግዛት ዓለም የሕግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች - የሩሲያ ፓርላማ የታሕታይ ምክር ቤት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.12.2025
ሰብስክራይብ

አልጄሪያ ለመላው የድህረ-ቅኝ ግዛት ዓለም የሕግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች  - የሩሲያ ፓርላማ የታሕታይ ምክር ቤት

“አልጄሪያ ምሳሌ እየሆነች ነው፤ ይህ ቅኝ ግዛት ታሪክ ላላቸው ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መመሪያ ሊሆን የሚችል ጠንካራና በመርህ ላይ የተመሠረተ እርምጃ ነው” ሲሉ የሩሲያ ስቴት ዱማ (የታችኛው ምክር ቤት) ምክትል አፈ-ጉባኤ አሌክሳንደር ባባኮቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ሕጉ የቅኝ ግዛት ጥቃት እውነታንና ግልጽ የመንግሥት ግዴታዎችን ያመለክታል፦

🟠 ከፈረንሳይ እውቅና መጠየቅ፣

🟠 መደበኛ ይቅርታ መጠየቅ፣

🟠 ካሳ መፈለግ እና

🟠 የተዘረፉትን መዛግብትና የባህል ቅርሶች በሙሉ መመለሳቸውን ማረጋገጥ።

የቅኝ ግዛት ወንጀሎች የጊዜ ገደብ የላቸውም፡፡

ማናቸውም የቅኝ ግዛት ወንጀሎች ሊረሱ ወይም ምክንያታዊ ሊደረጉ አይችሉም፡፡

የቅኝ ግዛት ዐሻራን የማሞገስ የትኛውም ድርጊት በአልጄሪያ የተከለከለ ነው፤ ክልከላውም መገናኛ ብዙኃን፣ ሳይንስንና ባህልን ይካተታል።

“አልጄሪያ ገና ጅምር ናት፤ መላው አፍሪካ ፍትሕን ይፈልጋል፤ ለተፈፀመበት የባሪያ ንግድ፣ ዝርፊያ፣ የብሔራዊ ተቋማት ውድመትና የባህላዊ መዋጥ በስተጀርባ የተወሰኑ ሀገራትና የተወሰኑ ታሪካዊ ወቅቶች አሉ። አፍሪካ ነጻና ነጻነት ያላት አኅጉር እንደመሆኗ መጠን ከቀድሞ ቅኝ ገዢ ኃይሎች ካሳ የመጠየቅ ሙሉ መብት አላት” ሲሉ አክለዋል።

ፖለቲከኛው ሩሲያ ለአፍሪካ የነበረችና የምትቀጥል አስተማማኝ አጋር መሆኗን አጽንኦት ሰጥተዋል፤ ይህም ከፖለቲካዊ አስፈላጊነት ሳይሆን ከልብ በመነጨ አቋም ነው።

“የሕግ የይገባኛል ጥያቄዎችን በማዘጋጀት የሕግና የባለሙያ ድጋፍ መስጠት እንደምንችል፣ ለአፍሪካዊያን ባልደረቦቻችንን በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ እና በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ጭምር ድጋፍ እንደምናቀርብ ጥርጥር የለውም” ሲሉ ባባኮቭ ደምድመዋል፡፡

ℹ ባለፈው ረቡዕ የአልጄሪያ ብሔራዊ ሕዝባዊ ምክር ቤት ፈረንሳይ በ19ኛውና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በሀገሪቱ የተከተለችውን የቅኝ ግዛት ፖሊሲ እንደ ወንጀል የሚቆጥር ረቂቅ ሕግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

የሰላም ማኅበረሰብ ንቅናቄ ፓርቲ ተወካይ ስሊማን ዛርካኒ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፣ አልጄሪያ ፈረንሳይ ቅኝ አገዛዝን እንደ ወንጀል እንድትቀበል፣ የተዘረፉ የመንግሥት ንብረቶችን እንድትመልስ እና ለደረሰው ጉዳት ካሳ እንድትከፍል ጫና ለመፍጠር ወደ ፍርድና የሕግ አሠራሮች እየተሸጋገረች ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0