ከእሁድ ለሰኞ አጥቢያ ፣ ኪዬቭ 91 የጥቃት ድሮኖችን በመጠቀም በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሽብር ጥቃት ፈጽማለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ገለጹ
18:26 29.12.2025 (የተሻሻለ: 18:44 29.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከእሁድ ለሰኞ አጥቢያ ፣ ኪዬቭ 91 የጥቃት ድሮኖችን በመጠቀም በሩሲያ ፕሬዝዳንት መኖሪያ ላይ የሽብር ጥቃት ፈጽማለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ገለጹ
የሩሲያ የአየር መከላከያ ስረዓቶች በኖቭጎሮድ ክልል በሚገኘውን የመኖሪያ ግቢ ላይ ጥቃት የፈፀሙትን ሁሉንም ድሮኖች ማውደማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቁልፍ መግለጫዎች፦
▪ ኪዬቭ ወደ መንግሥታዊ ሽብርተኝነት ፖሊሲ በመሸጋገሯ ምክንያት የሩሲያ የድርድር አቋም ክለሳይደረግበታል፡፡
▪ ኪዬቭ በኖቭጎሮድ ግዛት የሚገኘውን የፑቲን መኖሪያ በድሮኖች ለማጥቃት ሙከራ አድርጋለች፤ ሁሉም ድሮኖችም ተደምስሰዋል፡፡
▪ ኪዬቭ ጥቃቱን የፈጸመችው ሩሲያ እና አሜሪካ ግጭቱን ለመፍታት ከፍተኛ ድርድር እያደረጉ ባሉበት ወቅት ነው፡፡
▪ የኪዬቭ የግድየለሽነት እርምጃ ያለ አንዳች ምላሽ አይታለፍም፡፡
▪ የሩሲያ ጦር ኃይሎች የአጸፋ ጥቃት የሚፈጽሙባቸው ኢላማዎች እና ጥቃቱ የሚፈጸምበት ጊዜ ተወስኗል፡፡
▪ኪዬቭ ጥቃት ብትፈፅምም፣ ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር ከምታደርገው የድርድር ሂደት የመውጣት ፍላጎት የላትም።
የልዩ ዘመቻውን ዳራ ለመረዳት ስፑትኒክ አፍሪካ ያዘጋጀውን ትንታኔ ያንብቡ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X