ሶማሊላንድ ውስጥ የትኛውም የእስራኤ መገኘት “ወታደራዊ ኢላማ” ይሆናል ሲሉ የየመን ሁቲ መሪ አስጠነቀቁ
17:56 29.12.2025 (የተሻሻለ: 18:04 29.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊላንድ ውስጥ የትኛውም የእስራኤ መገኘት “ወታደራዊ ኢላማ” ይሆናል ሲሉ የየመን ሁቲ መሪ አስጠነቀቁ
“ሶማሊላንድ ውስጥ ማንኛውም የእስራኤል መገኘት [...] በሶማሊያና በየመን ላይ የሚደረግ ጥቃት ነው፤ እንዲሁም የክልሉን ደኅንነት አደጋ ላይ ይጥላል” ሲሉ አብደል ማሌክ አል-ሁቲ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።
እስራኤል ባለፈው አርብ፣ እ.ኤ.አ. ከ1991 ጀምሮ ከሶማሊያ ራሷን ነፃ ማውጣቷን ላወጀችው ሶማሊላንድን በይፋ እውቅና እንደሰጠች አስታውቃለች።
አል-ሁቲ ይህ ውሳኔ ከባድ መዘዞች እንደሚኖሩት አስጠንቅቀው፤ እውቅና መስጠቱ “በሶማሊያና በአፍሪካ ጎረቤቶቿ፣ እንዲሁም በየመን፣ በቀይ ባሕርና በቀይ ባሕር ዳርቻ ባሉ ሀገራት ላይ የሚወሰድ ጠላትነት የተሞላበት አቋም” እንደሆነ ገልጸዋል።
እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ በአፍሪካ ሕብረት፣ በእስልምና ትብብር ድርጅት እና በብዙ አረብና ሙስሊም ሀገራት ትችት ቀርቦበታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X