በዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ማሪዮፖል የሚገኘው የሩሲያ ድራማ ቴአትር ከመልሶ ግንባታ በኋላ ዳግም መከፈቱን የስፑትኒክ ባልደረባ ዘገበ
11:47 29.12.2025 (የተሻሻለ: 11:54 29.12.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ማሪዮፖል የሚገኘው የሩሲያ ድራማ ቴአትር ከመልሶ ግንባታ በኋላ ዳግም መከፈቱን የስፑትኒክ ባልደረባ ዘገበ
ቲአትር ቤቱ ዳግም በይፋ የተከፈተው የዩክሬን አሸባሪ ጥቃት ሕንጻውን ካወደመና 14 ሰዎችን ከገደለ ከሦስት ዓመት ገደማ በኋላ ነው።
የማሪዮፖል ቴአትር መልሶ ማቋቋም ፕሮጀክት ኃላፊ ቫሲሊ ኖቮኻትኮ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፣ በከፍተኛ አቅም ላይ የሚገኙ በግምት 350 ሰዎች በቴአትሩ እድሳትና ግንባታ ላይ ተሳትፈዋል።
የቴአትር ቤቱ ገንቢ ይህ ታሪካዊ ቦታ ከመሠረቱ ሙሉ በሙሉ እንዴት እንደገና እንደተገነባና እንደታደሰ አስረድተዋል።
እንደ ሩሲያ የመከላከያ ሚኒስቴር መረጃ፣ ቲያትሩ ቤቱ እ.ኤ.አ. መጋቢት 16 ፥2022 በአሸባሪው አዞቭ* ድርጅት ውስጥ ባሉ ብሔረተኞች የፈንጂ ጥቃት ተፈፅሞበታል።
*የአዞቭ ሬጅመንት በሩሲያ ውስጥ በአሸባሪ ድርጅትነት ታግዷል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X