የአፍሪካ ሕብረት ለሶማሊያ ድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ በመራዘሙ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች እስከ ታህሳስ 2019 በሱማሊያ ይቆያሉ ተባለ
15:06 28.12.2025 (የተሻሻለ: 15:14 28.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሕብረት ለሶማሊያ ድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ በመራዘሙ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች እስከ ታህሳስ 2019 በሱማሊያ ይቆያሉ ተባለ
የአፍሪካ ሕብረት እና የተመድ የፀጥታው ምክር ቤቶች፣ በሶማሊያ የሚገኘው የሰላም ማስከበር ጥረት ሥር በሰደደ የገንዘብ እጥረት ቢፈተንም፣ ተልዕኮ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም ወስነዋል።
ኢትዮጵያም በተሻሻለው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰላም አስከባሪ ኃይሏን በሶማሊያ ለማቆየት ተስማምታለች ሲል የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል።
በቅርቡ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ኢትዮጵያና ግብፅን ጨምሮ ሠራዊት የሚያዋጡ አገራት እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ 680 የፖሊስ አባላትን እና እስከ 11 ሺህ 826 የሚደርሱ ኃይሎችን በተልዕኮው ስር ማሰማራታቸውን ይቀጥላሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X