የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሊላንድ በሰጠችው እውቅና ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው
13:20 28.12.2025 (የተሻሻለ: 13:24 28.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሊላንድ በሰጠችው እውቅና ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው
ስብሰባው ለነገ መርሃ ግብር ተይዞለታል ሲሉ በተመድ የእስራኤል አምባሳደር ዳኒ ዳኖን አስታውቀዋል።
እስራኤል ባለፈው ሐሙስ ለሶማሊላንድ በይፋ እውቅና የሰጠች ሲሆን፣ ይህም እ.ኤ.አ. ከ1991 ጀምሮ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራሷን በራሷ ለምታስተዳድረው ሱማሌላንድ እውቅና የሰጠች በዓለም የመጀመሪያዋ ሀገር አድርጓታል።
ይህ የእስራኤል እርምጃ ሰፊ ዓለም አቀፍ ምላሾችን አስከትሏል። ሶማሊያ እውቅናውን በሉዓላዊነቷ ላይ የተፈጸመ "ሆን ተብሎ የተደረገ ጥቃት" ስትል በፅኑ አውግዛለች።
በተጨማሪም እንደ ባሕረ ሰላጤው የትብብር ምክር ቤት፣ የእስልምና ትብብር ድርጅት፣ የአፍሪካ ሕብረት እና የአውሮፓ ሕብረት ያሉ ዋና ዋና ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት በእስራኤል አካሄድ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X