የማርበርግ ቫይረስ በተከሰተበት አካባቢ በድሮን የታገዘ የመድኃኒት ስርጭት መጀመሩን የጤና ሚኒስትሯ አስታወቁ
12:59 28.12.2025 (የተሻሻለ: 13:04 28.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የማርበርግ ቫይረስ በተከሰተበት አካባቢ በድሮን የታገዘ የመድኃኒት ስርጭት መጀመሩን የጤና ሚኒስትሯ አስታወቁ
ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር መድኃኒቶችን እና የክትባት ስርጭቱን በደቡብ ኦሞ ወደ ምትገኘው የዳሰነች ወረዳ መላኩን ዶ/ር መቅደስ ዳባ በማኅበራዊ የትስስር ገፃቸው አስነብበዋል።
የዳሰነች ወረዳ ካለው ራቅ ያለ መልክዓ ምድር አኳያ በመኪና ለማጓጓዝ ረጅም ሠዓታት ይወስድ የነበረውን ጉዞ፣ በድሮን በመታገዝ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ክትባቱን በ –80 ዲግሪ ሴልሺየስ ቅዝቃዜ ጠበቆ በማድረስ ለአካባቢው ማኅበረሰብ ክትባቱን መስጠት ጀምሯል።
ሚኒስትሯ "ይህም ተግባር የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት (EPSS) የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ወረርሽኞችን ቀድሞ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገሩን በተግባር ያሳየበት ነው።" ብለዋል፡፡
በድሮን መድኃኒት የማድረስ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዶ/ር መቅደስ ዳባ ገልጸዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


