ሩሲያ አፍሪካ ውስጥ የአደጋ አስተዳደር ማዕከላትን ለማቋቋም እያጤነች ነው

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ አፍሪካ ውስጥ የአደጋ አስተዳደር ማዕከላትን ለማቋቋም እያጤነች ነው
ሩሲያ አፍሪካ ውስጥ የአደጋ አስተዳደር ማዕከላትን ለማቋቋም እያጤነች ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.12.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ አፍሪካ ውስጥ የአደጋ አስተዳደር ማዕከላትን ለማቋቋም እያጤነች ነው

​ማዕከላቱ ከእሳት አደጋ ተከላካዮች እና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች የሥልጠና ፕሮግራሞች ጋር በአንድነት በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 ሊተገበሩ ይችላሉ ሲል የሩሲያ የአደጋ ጊዜ ሁኔታዎች ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስትሩ አሌክሳንደር ኩሬንኮቭ እነዚህን ዕቅዶች በዛሬው ዕለት በተከበረው የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቀን ላይ ይፋ አድርገዋል።

​ ተነሳሽነቱ በርካታ የዓለም ቀጣናዎችን የሚያካትት ሲሆን አኅጉረ አፍሪካ፣ እስያ-ፓሲፊክ፣ መካከለኛው እስያ እና መካከለኛው ምሥራቅ ይገኙበታል።

​ሚኒስትሩ፣ የአደጋ ጊዜ ሁኔታዎችን ለመከላከል፣ መዘዞችን ለማስተዳደር እና ፈጣን የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

​ ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው፣ ተዛማጅነት ያላቸው ፕሮቶኮሎች አስቀድመው የተፈረሙ ሲሆን ከውጭ ኤጀንሲዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሚደረጉት ስምምነቶች በመጠናቀቅ ላይ ናቸው።

በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0