አሜሪካ በፈፀመችው የአየር ጥቃት ከአይኤስ* ጋር ግንኙነት ያላቸውን ካምፖች መምታቷን የናይጄሪያ መንግሥት አስታወቀ

አሜሪካ በፈፀመችው የአየር ጥቃት ከአይኤስ* ጋር ግንኙነት ያላቸውን ካምፖች መምታቷን የናይጄሪያ መንግሥት አስታወቀ
በፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ ፈቃድ በሶኮቶ ግዛት በሚገኘው ባውኒ ደን ላይ የተፈጸመው ጥቃት፤ ሰፊ የመረጃ ማሰባሰብ እና እቅድ ከተሰራ በኋላ ሐሙስ ዕለት በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ከሚገኙ የባሕር ሰፈሮች መጀመሩን የኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር ገልጿል።
ከኤምኪው-9 ሪፐር ሰው አልባ አውሮፕላኖች የተተኮሱ 16 በጂፒኤስ የሚመሩ ሚሳኤሎች ከሳሕል ቀጣና ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት የሚሞክሩ ከአይኤስ (ISIS) ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኢላማዎች ደምስሰዋል። የናይጄሪያ መንግሥት እንደገለጸው፣ የደህንነት መረጃዎች እነዚህ ካምፖች መጠነ-ሰፊ ጥቃቶችን ለማድረስ ሲያቅዱ እንደነበር ያመለክታሉ። በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት ባይኖርም፤ የጥቃቱ ፍርስራሾች ግን በሶኮቶ እና በኳራ ግዛቶች ውስጥ ወድቀዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው በናይጄሪያ ጥያቄ መሰረት መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ ድርጊቱን "ተከታታይ ስኬታማ ጥቃቶች" ሲሉ ጠርተውታል። ተጨማሪ እርምጃዎች ሊከተሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።
የሶኮቶ ግዛት ባለሥልጣናት ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ ጥቃቱ የሰዎችን ሕይወት እና ንብረት ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን በመግለጽ ነዋሪዎች እንዲረጋጉ አሳስበዋል።
*ዳኢሽ (አይኤስ) በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት የታገደ የአሸባሪ ቡድን ነው።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X