በኮት ዲቯር የፓርላማ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ሂደት መጀመሩ ተዘገበ
14:07 27.12.2025 (የተሻሻለ: 14:14 27.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኮት ዲቯር የፓርላማ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ሂደት መጀመሩ ተዘገበ
በሀገሪቱ ብሔራዊ ምክር ቤት ለሚገኙ 255 መቀመጫዎች በድምሩ 1 ሺህ143 እጩዎች እየተወዳደሩ ይገኛሉ። ድምፅ የመስጠት ሂደቱም በ11 ሺህ 835 የምርጫ ጣቢያዎች እየተከናወነ ይገኛል።
የምርጫውን ሰላማዊ ሂደት ለማረጋገጥ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ መምሪያ 44 ሺህ የጦር ሰራዊት እና የፖሊስ አባላትን ያሳተፈ "ኦፕሬሽን ሲቪል ዶም" የተሰኘ ዘመቻ ጀምረዋል። ይህ የደህንነት ጥበቃ ዘመቻ እስከ ታህሳስ 4 ይቆያል።
የመጀመሪያዎቹ የቅድመ ውጤቶች በነገው ዕለት ይፋ ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X