የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ውድቅ አደረጉ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ውድቅ አደረጉ
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ውድቅ አደረጉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.12.2025
ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ውድቅ አደረጉ

መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ ለሶማሊያ አንድነት እና ሉዓላዊነት ያላቸውን ጽኑ አቋምም በድጋሚ አረጋግጠዋል ሲል ሕብረቱ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

ሊቀመንበሩ ሶማሊላንድ የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የማትነጠል አካል መሆኗን በማስታወስ፣ ሶማሊላንድን እንደ ገለልተኛ አካል እውቅና ለመስጠት የሚደረግ ማንኛውንም ተነሳሽነት ወይም እርምጃ በፅኑ ውድቅ አድርገዋል።

“የሶማሊያን አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማፍረስ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ፣ ከአፍሪካ ሕብረት መሠረታዊ መርሆች ጋር የሚቃረን እና በመላ አኅጉሪቱ ሰላም እና መረጋጋት ላይ ትልቅ እንድምታ ያለው አደገኛ ምሳሌ ሊሆን ይችላል።” ብለዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0