ከ33ኛ ወደ 4ኛ – ቻይና የኢትዮጵያ ቡና ቁልፍ መዳረሻ ሆናለች
11:24 27.12.2025 (የተሻሻለ: 11:34 27.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከ33ኛ ወደ 4ኛ – ቻይና የኢትዮጵያ ቡና ቁልፍ መዳረሻ ሆናለች
ቻይና የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት ከ5 ዓመት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ በተያዘው ዓመት ወደ 4ኛ ደረጃ ከፍ በማለት የኢትዮጵያ ቡና ዋና መዳረሻ ሀገር መሆኗ የአገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ቡናን በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ፤ ገበያ ለመፈለግና ኤክስፖርቱን ለማሳደግ ዓላማ ያደረገ ኮንፈረንስ በቻይና ሁናን ግዛት እየተካሄደ መሆኑንም ዘገባው አመላክቷል።
የኢትዮ-ቻይና የወዳጅነት ኮሚቴ ባዘጋጀው ይህ ኮንፈረንስ ከ700 ሺህ በላይ ሰዎች የኢትዮጵያን ባለልዩ ጣዕም ቡና ለማስቀመስ እቅድ ተይዟል።
በኮንፍረንሱ የጁጆ ከተማን ከንቲባ ጨምሮ የቻይና ከፍተኛ አመራሮች እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ተሳታፊ ሆነዋል።
ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ከ35 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለቻይና ገበያ ማቅረቧንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



