አል-ቡርሃን በሱዳን ሰላም እንዲሰፍን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ለፈጥኖ ደራሽ ኃይል የምታደርገውን ድጋፍ እንድታቆም ጠየቁ
20:37 26.12.2025 (የተሻሻለ: 20:54 26.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አል-ቡርሃን በሱዳን ሰላም እንዲሰፍን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ለፈጥኖ ደራሽ ኃይል የምታደርገውን ድጋፍ እንድታቆም ጠየቁ
የሱዳን መሪ አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን እና ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በመካከለኛው ምስራቅ እና በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ለመምከር ትናንት በአንካራ ተገናኝተዋል።
በዘገባዎች መሠረት በሱዳን እና በቱርክ መሪዎች ውይይት የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች፦
ሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ከከተሞች እንዲወጡ፣ በተለዩ ካምፖች እንዲሰባሰቡ እና ትጥቅ እንዲፈቱ ትጠይቃለች።
ይህ ከተከናወነ በኋላ ስለ ሀገሪቱ አስተዳደር እና ምርጫ ብሔራዊ ውይይት ይደረጋል።
የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ምንም ዓይነት የፖለቲካም ይሁን የኢኮኖሚ ሚና አይኖረውም።
በሱዳን ሕዝብ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እንዲቆሙ እና ፈፃሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ አጽንኦት ተሰጥቷል።
አንካራ በቱርክ የትብብር እና ቅንጅት ኤጀንሲ በኩል ለሱዳን ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/