“የእንሰት ተክል በአሁኑ ሰዓት በበሽታ እየተጎዳ ይገኛል” - የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢኒስትቲዩት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ“የእንሰት ተክል በአሁኑ ሰዓት በበሽታ እየተጎዳ ይገኛል” - የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢኒስትቲዩት
“የእንሰት ተክል በአሁኑ ሰዓት በበሽታ እየተጎዳ ይገኛል” - የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢኒስትቲዩት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.12.2025
ሰብስክራይብ

“የእንሰት ተክል በአሁኑ ሰዓት በበሽታ እየተጎዳ ይገኛል” - የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢኒስትቲዩት

የሀገሪቱን የጄኔቲክ ሀብቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች በመጠበቅ ረገድ ክፍተት መኖሩ ለችግሩ መንስዔ እንደሆነ በኢኒስትቲዩቱ የአዝርዕትና ሆርቲካልቸር ምርምር መሪ ሥራ ሂደት አስፈጻሚ ውብሸት ተሾመ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

“አንዳንድ የጄኔቲክ ሀብቶች ዘመናዊ በሆኑ ቴክኖሎጂዎች መጠበቅ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ የሚመገበው የእንሰት ተክል በአሁኑ ሰዓት በበሽታ እየተጎዳ ይገኛል።...ዲኤንኤውን ብቻ አውጥተን ልንጠብቅ ይገባ ነበር። ይህ ቴክኖሎጂ ወደ ኢንስቲትዩቱ ባለመግባቱ እንደዚህ አይነት የጄኔቲክ ሀብቶች እየተመናመኑ፣ እየተጎዱብን ይገኛሉ” ብለዋል።

በሌላ በኩል ባለፉት ሰባት ዓመታት ተግባራዊ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር የጠፉ ዝርያዎችን በመመለሱ በኩል አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

“መልካም አጋጣሚ የምንላቸው ለምሳሌ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን እየተገበረ ይገኛል። ይሄ የጠፉ ዝርያዎችን በመተካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። ስለዚህ ይሄ ጥሩ አጋጣሚ ነው እላለሁ።”

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0