በኢትዮጵያ ሁሉም ክልሎች ለሚገኙ 17 ቅርሶች የጥበቃ እና እንክብካቤ ሥራ ለመሥራት መታቀዱ ተገለፀ
17:04 26.12.2025 (የተሻሻለ: 18:54 26.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ ሁሉም ክልሎች ለሚገኙ 17 ቅርሶች የጥበቃ እና እንክብካቤ ሥራ ለመሥራት መታቀዱ ተገለፀ
በአማራ፣ በትግራይ፣ በአፋር፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሀረር ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ ለሚገኙ ቅርሶች፤ በተያዘው በጀት ዓመት ጥበቃና እንክብካቤ ለማድረግ እቅድ መቀመጡን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡
ጥበቃ እና እንክብካቤ ሊደረግላቸው የታሰቡት ቅርሶች ዓለም አቀፍ፣ ሀገር አቀፍ እና ታሪካዊ ቅርሶች ናቸው ተብሏል፡፡
በተያያዘም 10 ለሚሆኑ ቅርሶች የቅድመ ጥገና ጥናት ለማድረግ ሂደት መጀመሩን ባለሥልጣኑን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


