ሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሞቃዲሾ የቀጥታ ምርጫ እያካሄደች ነው
16:22 25.12.2025 (የተሻሻለ: 16:24 25.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሞቃዲሾ የቀጥታ ምርጫ እያካሄደች ነው
የሶማሊያ መዲና ነዋሪዎች ዛሬ ለማዘጋጃ ቤት ምርጫ በቀጥታ ድምፅ እየሰጡ ይገኛሉ። ምርጫው እ.ኤ.አ ከ1969 ጀምሮ በጎሳ ላይ የተመሠረተ የውክልና የምርጫ ሥርዓት ስትከተል በቆየችው ሀገር የዜጎችን የመምረጥ መብት ዳግም የሚመልስ ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ታይቷል።
ከአል-ሸባብ ታጣቂዎች ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን ለመከላከል 10 ሺህ የሚጠጉ የፀጥታ ኃይሎች ተሠማርተው ጥብቅ የፀጥታ ቁጥጥር እየተካሄደ ነው።
በቅርቡ በተደረገ ፖለቲካዊ ስምምነት መሠረት እ.ኤ.አ በ2026 የፓርላማ አባላት በቀጥታ በሕዝብ ድምፅ እንዲመረጡ ቢወሰንም ፕሬዝዳንቱ ግን በፓርላማ አባላት መመረጣቸው ይቀጥላል።
ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኙ ምሥሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



