በኢትዮጵያ የተመረቱ የማዕድን ማቀነባበሪያ ማሽኖች ወደ ሥራ ሊገቡ መሆኑ ተገለፀ
15:34 25.12.2025 (የተሻሻለ: 15:44 25.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የተመረቱ የማዕድን ማቀነባበሪያ ማሽኖች ወደ ሥራ ሊገቡ መሆኑ ተገለፀ
በሀገር ውስጥ የተመረቱት የማዕድን መቁረጫ፣ የማለስለሻና የቅርጽ ማውጫ ማሽኖች በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ የማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
ኢንስቲትዩቱ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ያመረታቸው ማሽኖች የጌጣጌጥ ማዕድናት ላይ እሴት ጨምሮ በማምረት የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ እንደሚያስችሉ ተመላክቷል፡፡
ዘርፉን በዘመናዊ ስርዓት ለመምራት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንባታ እየተከናወነ እንደሆነ እና የማዕድን ማውጫ አደጋን የሚከላከል የደህንነት ምሰሶ ዲዛይን እና የኢትዮጵያ የጌጣጌጥ ማዕድናት ልማት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት በመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X