በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ257 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ሰብዓዊ እርዳታ አሰራጭቻለሁ - የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን
12:01 25.12.2025 (የተሻሻለ: 12:04 25.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ257 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ሰብዓዊ እርዳታ አሰራጭቻለሁ - የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን
ሰብዓዊ እርዳታ እየደረሰ አይደለም ተብሎ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የቀረበው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ገልጿል።
ባለፉት አራት ወራት 11 ሺህ 406 ኩንታል ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጥራጥሬ እንዲሁም የምግብ ዘይት በትግራይ ክልል ሰሜን ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ "ህፃፅ" ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ማሠራጨቱን ኮሚሽኑ አስታውቋል።
ከመስከረም እስከ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም ባሉት ወራት ውስጥ ለተፈናቃዮቹ ያልተቋረጠ የምግብ እርዳታ ሲደረግ መቆየቱንም በመግለጫው ጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X