ዓለም አቀፍ ተቋማት የራሳቸውን ጥቅም እንጂ ፍትሕን ወይም እኩልነትን አያስጠብቁም - ናይጄሪያዊ ተሟጋች

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፍ ተቋማት የራሳቸውን ጥቅም እንጂ ፍትሕን ወይም እኩልነትን አያስጠብቁም - ናይጄሪያዊ ተሟጋች

ናይጄሪያዊው ነጋዴ እና ተሟጋች ኦላዴል ዶሱንሙ እንደ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት፣ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም፣ የዓለም ባንክ እና የዓለም ንግድ ድርጅት ያሉ ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ተቋማትን አጥበቀው ተችተዋል።

"ስርዓቱ የተዋቀረው የፈጠሩትን ክፋት ለመጠበቅ ነው" ሲሉ የአልኬቡላን ኢኖቬሽን ፋውንዴሽን መሥራች የሆኑት ዶሱንሙ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እንደቀድሞው የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ቻርለስ ቴይለር ያሉ ታዋቂ ግለሰቦችን ክስ አንስተው፤ አይሲሲ ሌሎች ዓለም አቀፍ ግጭቶችን ከሚይዝበት ሁኔታ ጋር በማነፃፀር የሚያራምደውን የድርብ መስፈርት አካሄድ ጠቅሰዋል።

"የእስራኤልን ጉዳይ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል ማየት ነው፣ ምን እንደተፈጠረ መመልከት ነው፣ ያደረጉትን ተመልከቱ፣ እንዴት እንዳደናቀፉት ተመልከቱ" ብለዋል።

አሁን ባለው መዋቅር እውነተኛ ተጠያቂነት የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም እነሱ የፈጠሯቸው ሥርዓቶች እነሱን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን 'ክፋታቸውን' ለመከላከል የቆሙ ናቸው ሲሉ ዶሱንሙ ንግግራቸውን አጠቃለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0