በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በሚገኝ መስጂድ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ
11:03 25.12.2025 (የተሻሻለ: 11:04 25.12.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በሚገኝ መስጂድ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ
ፍንዳታው የተከሰተው በማይዱጉሪ ከተማ በሚገኝ አንድ መስጂድ ውስጥ የምሽት ጸሎት እየተካሄደ በነበረበት ወቅት መሆኑን መገናኛ ብዙኃን ረቡዕ እለት ባወጡት ዘገባ አመላክተዋል፡፡
በከተማው የገበያ ቦታ በሚገኝ መስጂድ ተጠምደው የነበሩ ቤት ውስጥ የተሠሩ ፈንጂዎች በግምት ከምሽቱ 2:00 ሰዓት አካባቢ እንደፈነዱ ተገልጿል።
'የቦምብ ጥቃት ሳይሆን አይቀርም' ለተባለው ጥቃት፤ እስካሁን የትኛውም የታጠቀ ቡድን ኃላፊነቱን አልወሰደም።
ℹ የቦርኖ ግዛት ዋና ከተማ የሆነችው ማይዱጉሪ፤ እንደ ቦኮ ሃራም እና የእሱ ተገንጣይ የምዕራብ አፍሪካ የእስልምና መንግሥትን ያሉ ጂሃዳዊ ቡድኖች የሚሳተፉበት የረጅም ጊዜ አመጽ ማዕከል ሆና ቆይታለች። ይሁን እንጂ ከተማዋ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከባድ ጥቃት አስተናግዳ አታውቅም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X