ሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሩሲያ ኤምባሲ ዘገባውን በፅኑ በማስተባበል፤ በቅጥረኞች ዙሪያ የፈረንሳይን ታሪካዊ አባይነት በመጥቀስ ከሷል።
የኤምባሲው መግለጫ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ታግዶ በሚገኘው የ "አርኤፍአይ" ዘገባ በፈረንሳዊው የደህንነት ባለሙያ ቲዬሪ ቪርኩሎን የተሠነዘሩትን የተወሰኑ ክሶች ጠቅሷል።
የዲፕሎማሲ ተልዕኮው ክሶቹን በዩክሬን ግጭት ላይ “ሚዛናዊ አቋም” ከያዙት የአፍሪካ ሀገራት ጋር ያለውን የሩሲያን ወዳጃዊ ግንኙነት ለመጉዳት የታሰቡ “መሠረት ቢስ” ፈጠራዎች ብሏቸዋል።
ኤምባሲው ክሱን ፓሪስ ላይ በማዞር፤ የሀገሪቱን ታሪካዊ ድርጊቶች እንደሚከተለው ጠቅሷል፡-
የፈረንሳይ የውጭ ወታደራዊ ኃይል ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የቀድሞ የናዚ ወታደሮችን መልምሏል።
እንደ ቦብ ዴናርድ ያሉ ዘመናዊ የፈረንሳይ ቅጥረኞች በቀድሞ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች በዘመቻዎች ተሳትፈዋል።
በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ ቅጥረኞች ለዩክሬን እየተዋጉ እንደሆኑ የሚጠቁሙ ሪፖርቶች መኖራቸውን በመጥቀስ፤ ይህ በፈረንሳይ ሕግ ወንጀል መሆኑን ኤምባሲው አመልክቷል።
ኤምባሲው ይህ “ሐሰተኛ ዜና” የወጣበት ጊዜ ከካይሮው የሩሲያ-አፍሪካ ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ጋር መገጣጠሙ ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሆነ ጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X