ሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች
ሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.12.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ አፍሪካውያንን ለዩክሬን ውጊያ እየመለመለች ነው በሚል በፈረንሳይ ሚዲያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሩሲያ ኤምባሲ ዘገባውን በፅኑ በማስተባበል፤ በቅጥረኞች ዙሪያ የፈረንሳይን ታሪካዊ አባይነት በመጥቀስ ከሷል።

የኤምባሲው መግለጫ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ታግዶ በሚገኘው የ "አርኤፍአይ" ዘገባ በፈረንሳዊው የደህንነት ባለሙያ ቲዬሪ ቪርኩሎን የተሠነዘሩትን የተወሰኑ ክሶች ጠቅሷል።

የዲፕሎማሲ ተልዕኮው ክሶቹን በዩክሬን ግጭት ላይ “ሚዛናዊ አቋም” ከያዙት የአፍሪካ ሀገራት ጋር ያለውን የሩሲያን ወዳጃዊ ግንኙነት ለመጉዳት የታሰቡ “መሠረት ቢስ” ፈጠራዎች ብሏቸዋል።

ኤምባሲው ክሱን ፓሪስ ላይ በማዞር፤ የሀገሪቱን ታሪካዊ ድርጊቶች እንደሚከተለው ጠቅሷል፡-

የፈረንሳይ የውጭ ወታደራዊ ኃይል ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የቀድሞ የናዚ ወታደሮችን መልምሏል።

እንደ ቦብ ዴናርድ ያሉ ዘመናዊ የፈረንሳይ ቅጥረኞች በቀድሞ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች በዘመቻዎች ተሳትፈዋል።

በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ ቅጥረኞች ለዩክሬን እየተዋጉ እንደሆኑ የሚጠቁሙ ሪፖርቶች መኖራቸውን በመጥቀስ፤ ይህ በፈረንሳይ ሕግ ወንጀል መሆኑን ኤምባሲው አመልክቷል።

ኤምባሲው ይህ “ሐሰተኛ ዜና” የወጣበት ጊዜ ከካይሮው የሩሲያ-አፍሪካ ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ጋር መገጣጠሙ ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሆነ ጠቁሟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0