ኦፓል መሰል ማዕድናት ወደ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እንዲገቡ መደረጉ ሕገ-ወጥ ንግድን በማስቀረት፤ ለአምራቾች ፍትሐዊ ዋጋ ያረጋግጣል - የዘርፉ ባለሙያ
15:55 24.12.2025 (የተሻሻለ: 16:04 24.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኦፓል መሰል ማዕድናት ወደ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እንዲገቡ መደረጉ ሕገ-ወጥ ንግድን በማስቀረት፤ ለአምራቾች ፍትሐዊ ዋጋ ያረጋግጣል - የዘርፉ ባለሙያ
እርምጫው ደላሎችን እና የኮንትሮባንድ ዝውውርን የሚስቀር ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ መደበኛ የኦፓል ግብይት ሊያስጀምር እንደሆነ መግለጹን አስመልክቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ አሰትያየታቸውን የሰጡት የማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬከተር ብስራት ከበደ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
“መደበኛ የዋጋ አወሳሰን ስርዓቶችን መዘርጋት፣ አምራቾች መደበኛ ባልሆኑ ደላሎች ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ይቀንሳል። ግብይቶችን በዲጂታል ዘዴ በመከታተል፣ የኮንትሮባንድ ዝውውርን በቀላሉ መለየት ያስችላል። በተጨማሪም የኦፓል አምራቾች ፍቃድ ካላቸው ላኪዎች ጋር በቀጥታ በመገናኘት እና ተወዳዳሪ የዋጋ ጨረታዎችን በማግኘት፣ ከዓለም አቀፍ የገበያ ደረጃዎች ጋር የተጣጣመ ፍትሐዊ ዋጋ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።”
ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት የዘለለ ራዕይ አንግባ ያለቁ የከበሩ ድንጋዮች አቅራቢ የመሆን የረጅም ግዜ ዕቅድ እንዳላትም ባለሙያው ገልፀዋል፡፡
“እንደ ስልታዊ ዕቅድ የተያዘው እሴት ለተጨመረባቸው የወጪ ንግዶች ማበረታቻ መስጠት ነው፡፡...ለጊዜው ኢትዮጵያ የገበያ ተደራሽነትን በማረጋገጥ እና የሀገር ውስጥ የማቀነባበር አቅምን እያሳደገች፤ ጥሬ እና ያለቁ ኦፓሎችን ለመገበያየት የኢትዮጵያ ምርት ገበያን ትጠቀማለች። የረጅም ጊዜ ራዕዩ ኢትዮጵያን ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ ያለቁ የከበሩ ድንጋዮች አምራችነት በማሸጋገር፤ በብሪክስ እና በዓለም አቀፍ ገበያዎች ውስጥ ተወዳዳሪ ሆና እንድትገኝ ማድረግ ነው።”
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X