ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚያግደው መመሪያ ከጥር 23 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚያግደው መመሪያ ከጥር 23 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ
ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚያግደው መመሪያ ከጥር 23 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.12.2025
ሰብስክራይብ

ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚያግደው መመሪያ ከጥር 23 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ

የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትና ይዞ መገኘት የሚከለክለው አዋጁ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ መጽደቁ ይታወሳል፡፡ ባለሥልጣኑ የስድስት ወራት ሽግግር ጊዜ መስጠቱም የሚታወቅ ነው፡፡

የሽግግር ጊዜው ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያበቃ የገለጹት የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዴስክ ኃላፊ ዋሲሁን ዓለሙ፤ ከዚህ ዕለት በኋላ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙ አካላት ተጠያቂ እንደሚሆኑ አሳስበዋል።

አዋጁ እንደወጣ የፕላስቲክ ስርጭት ቀንሶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ግን በድጋሚ በገበያው ውስጥ በስፋት እየታየ ነውም ተብሏል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0