የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በመጪው ጥር ወር መጨረሻ ይደረጋል ተባለ
15:04 23.12.2025 (የተሻሻለ: 15:24 23.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በመጪው ጥር ወር መጨረሻ ይደረጋል ተባለ
ኮሚሽኑ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰጠው የሥራ ጊዜ እስከ የካቲት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ድረስ ነው። በዚህም መሠረት ለዋናው ጉባዔ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችና የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከወዲሁ እየተከናወኑ መሆኑን ኮሚሽነሩ መስፍን አርዓያ ለሚዲያ አስረድተዋል።
ከ4 ሺህ በላይ ተወካዮች በጉባዔው ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ከትግራይ በስተቀር በሁሉም አካባቢዎች አጀንዳዎችን የማሰባሰብና ተሳታፊዎችን የመለየት ሥራዎችን አከናውኗል።
በትግራይ ክልል የተሳታፊዎች ልየታ፣ የአጀንዳ ማሰባሰብ እና ተወካዮችን የማስመረጥ ሥራዎች ቅደመ ዝግጀት በያዝነው ሳምንት እንደሚጀመር እና የምክክር ሥራው እስከ ታህሳስ 30 ቀን እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል ሲሉም ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X