ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልማት ለማፋጠን እና የሥራ ዕድል ለመፍጠር በኪንሻሳ ግዙፍ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ይፋ አደረገች
14:35 23.12.2025 (የተሻሻለ: 14:44 23.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልማት ለማፋጠን እና የሥራ ዕድል ለመፍጠር በኪንሻሳ ግዙፍ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ይፋ አደረገች
አዲሱ ከተማ "ኪንሻሳ ኪያ ሞና" (የኪንሻሳ ህዳሴ)፤ በኮንጎ ዋና ከተማ ምሥራቃዊ ክፍል በሚገኘው ማሉኩ ኮሙን በ43 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ይገነባል ሲል የኮንጎ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
የከተማ ፕላን እና ቤቶች ሚኒስትሩ አሌክሲስ ጊሳሮ ሙቩንዪ በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሲናገሩ፤ "ይህ ፕሮጀክት ትልቅ ፖለቲካዊ እርመጃ እና እርግጥ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ አሳጣጥን የሚወክል እና ከሁሉም በላይ ካለፈው ያልተደራጀና ውጤት አልባ የሲቪል ከተማ ልማት ጋር የተለየ ነው" ብለዋል።
ስለ ፕሮጀክቱ ተጨማሪ ዝርዝሮች፦
🟠 አዲሱ የኪንሻሳ ማስፋፊያ የትራፊክ መጨናነቅን እና የቤት እጦትን እንደሚያቃልል የኪንሻሳ አስተዳዳሪ ተናግረዋል።
🟠 12 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የኢንዱስትሪ ዞን ይኖረዋል።
🟠 155 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ሁለገብ የሆስፒታል ሕንጻ በውስጡ ይገነባል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

