ሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቷን አጠናቀቀች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቷን አጠናቀቀች
ሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቷን አጠናቀቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.12.2025
ሰብስክራይብ

ሶማሊያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቷን አጠናቀቀች

በመጪው ሐሙስ በሞቃዲሾ የሚካሄደውን የማዘጋጃ ቤት ምርጫ ደህንነት ለማረጋገጥ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉ የፖሊስ መኮንኖች ይሠማራሉ።

የሶማሊያ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር አብዱላሂ ሼክ ኢስማኢል፤ አስፈላጊው ዝግጅት በሙሉ ሙሉ "ተጠናቋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የፖሊስ መኮንኖች የመራጮችን፣ የምርጫ ጣቢያዎችን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን እና ለአደጋ ተጋላጭ መሠረተ ልማቶችን ደህንነት ለማረጋገጥ በዋና ከተማው እንደሚሠማሩ አብራርተዋል።

ምርጫው በአንድ ሰው አንድ ድምጽ መርህ ላይ ተመሥርቶ በሞቃዲሾ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ የሚካሄድ ቀጥተኛ ምርጫ ነው። በምርጫው ከ1 ሺህ 600 በላይ ዕጩዎች ለ390 የአካባቢ መቀመጫዎች ይወዳደራሉ። ወደ 400 ሺህ የሚጠጉ የተመዘገቡ መራጮች ይመርጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሊያ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0