የጊኒ -ቢሳው የሥልጣን ሽግግር - ሴኔጋል መረጋጋትን ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት እየመራች ነው
17:59 22.12.2025 (የተሻሻለ: 18:04 22.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጊኒ -ቢሳው የሥልጣን ሽግግር - ሴኔጋል መረጋጋትን ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት እየመራች ነው
የጊኒ ቢሳው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ የሴኔጋል የውጭ ጉዳይ እና የመከላከያ ሚኒስትሮች ከሽግግሩ መሪ ጄኔራል ሆርታ ንታም ጋር ለመገናኘት ወደ ቢሳው ተጉዘዋል።
የሴኔጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቼክ ኒያንግ "የፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማይ ፋዬን መልዕክት ይዘው" መምጣታቸውን ገልጸዋል።
ቼክ ኒያንግ ከውይይቱ በኋላ በሰጡት መግለጫ "ሴኔጋል ለጊኒ ቢሳው የምታደርገውን ድጋፍ ለመቀጠል እና በተቻለ ፍጥነት ወደ መደበኛ ሁኔታ መመለሱን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት ለመግለጽ መጥታለች" ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ልዑኩ ከህዳር 16 ክስተቶች በኋላ የታሰሩ ግለሰቦች በሙሉ እንዲፈቱ ሀሳብ አቅርቧል።
"ጊኒ ቢሳው በመጀመሪያ ከምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ፣ ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከተመድ እና ከሌሎች ድርጅቶች ዓለም አቀፍ ድጋፍ ማግኘቷ አስፈላጊ ነው" ሲሉ የሴኔጋሉ ሚኒስትር አክለዋል።
የህዳር 16 የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ሊገለጽ 24 ሰዓታት ሲቀረው፣ በጄኔራል ሆርታ ንታም የሚመራ የወታደሮች ቡድን ስልጣን መያዙ ይታወሳል። የምርጫው ውጤትም እስካሁን ይፋ አልተደረገም።
በወታደራዊ ኃይሉ ለጥቂት ጊዜ ታስረው የነበሩት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡማሮ ሲሶኮ ኢምባሎ፣ በኋላ ላይ ተለቅቀው ወደ ሴኔጋል ተወስደዋል። በህዳር 13ቱ ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚሉት የተቃዋሚው እጩ ፈርናንዶ ዲያስ ዳ ኮስታ በቢሳው በሚገኘው የናይጄሪያ ኤምባሲ ተጠልለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X