የናይጄሪያ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የመጨረሻዎቹ 130 በእገታ ላይ የቆዩ ተማሪዎችና መምህራን ሙሉ በሙሉ መለቀቃቸውን አስታወቀ
16:05 22.12.2025 (የተሻሻለ: 16:14 22.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የመጨረሻዎቹ 130 በእገታ ላይ የቆዩ ተማሪዎችና መምህራን ሙሉ በሙሉ መለቀቃቸውን አስታወቀ
የፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን አማካሪ ሰንደይ ዳሬ እንደገለጹት፤ አሁን የተለቀቁት 130 ተማሪዎች፣ ህዳር 12 በኒጀር ግዛት ከሚገኘው ሴንት ሜሪ የካቶሊክ ትምህርት ቤት በታጣቂዎች ታፍነው ከነበሩት 303 ተማሪዎች እና 12 የትምህርት ቤቱ ሠራተኞች መካከል የመጨረሻዎቹ ናቸው።
የእነዚህ ተማሪዎች መለቀቅ ቀደም ብለው ከተከናወኑ ሂደቶች አካል ነው፡፡ ከታፈኑት ውስጥ 50 ተማሪዎች ወዲያውኑ ማምለጥ የቻሉ ሲሆን፣ ሌሎቹን 100 ተማሪዎች ደግሞ ህዳር 29 የደህንነት ኃይሎች እንደታደጓቸው ይታወሳል።
የግዛቱ ገዥ መሐመድ ባጎ ሕፃናቱን በሚና በሚገኘው የመንግሥት ግቢ ውስጥ የተቀበሏቸው ሲሆን፤ የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ልጆቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ከመቀላቀላቸው በፊት የሕክምና ምርመራ ይደረግላቸዋል።
ምንም እንኳን የግዛቱ አስተዳደር ትምህርት ቤቱን የደህንነት ስጋት ባለበት ሁኔታ ዳግም በመክፈቱ መጀመሪያ ላይ ቢወቅስም፤ አሁን የተገኘው የተሳካ የማዳን እርምጃ ለፕሬዝዳንት ቲኑቡ አስተዳደር ትልቅ ድል ተደርጎ ተቆጥሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/