ሩሲያ የቀድሞዋን የሶቪዬት ሕብረት ተፅዕኖ ወደ ነበረበት ለመመለስ እያቀደች ነው የሚሉ ዘገባዎች እውነት አይደሉም ሲሉ የክሪሚሊን ቃል አቀባይ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ የቀድሞዋን የሶቪዬት ሕብረት ተፅዕኖ ወደ ነበረበት ለመመለስ እያቀደች ነው የሚሉ ዘገባዎች እውነት አይደሉም ሲሉ የክሪሚሊን ቃል አቀባይ ተናገሩ
ሩሲያ የቀድሞዋን የሶቪዬት ሕብረት ተፅዕኖ ወደ ነበረበት ለመመለስ እያቀደች ነው የሚሉ ዘገባዎች እውነት አይደሉም ሲሉ የክሪሚሊን ቃል አቀባይ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.12.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ የቀድሞዋን የሶቪዬት ሕብረት ተፅዕኖ ወደ ነበረበት ለመመለስ እያቀደች ነው የሚሉ ዘገባዎች እውነት አይደሉም ሲሉ የክሪሚሊን ቃል አቀባይ ተናገሩ

ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ ክሬምሊን እንዲህ ያሉ ዘገባዎችን አይቶ እንደሆነና በጉዳዩ ላይ ያለውን አስተያየት ለጋዜጠኞች ሲገልጹ፤ ዘገባዎቹ ምን ያህል ተዓማኒ እንደሆኑ ክሬምሊን እንደማያውቅ አስረድተዋል።

"ስለዚህ ጉዳይ የተበታተኑ ዘገባዎችን አይተናል፤ ነገር ግን ዘገባዎቹ እውነት ቢሆኑ እንኳ፣ ይህ የመረጃ ተቋማት የተሳሳተ አመክንዮ፣ ምርመራ እና ድምዳሜ ላይ የሚደርሱበት ዓይነት ሁኔታ ነው። መረጃው ፍጹም ከእውነት የራቀ ነው" ብለዋል።

ቀደም ብሎ አንድ የእንግሊዝ የሚዲያ የአሜሪን የደህንነት ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ፣ ፑቲን "መላዋን ዩክሬንን የመቆጣጠር እና ቀደም ሲል የቀድሞው የሶቪዬት ግዛት አካል የነበሩ የአውሮፓ ክፍሎችን መልሶ የመያዝ ዓላማ አላቸው" ሲል ገልጾ ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0