ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ
ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.12.2025
ሰብስክራይብ

ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ

የዩክሬን ብሔራዊ ደህንነትና መከላከያ ምክር ቤት ጸሐፊ ሩስቴም ኡሜሮቭ፣ በዩክሬን ብሔራዊ ፀረ-ሙስና ቢሮ ከሚካሄድባቸው ምርመራ ከለላ ይሰጧቸው ዘንድ ለአሜሪካ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ዳይሬክተር ካሽ ፓቴልን መጠየቃቸውን ድዜራኬሎ ታይዝንያ ዘግቧል።

የዜና አውታሩ እንደገለጸው፣ “በኡሜሮቭ እና በካሽ ፓቴል መካከል የተደረገው ውይይት በዩክሬን፣ በአሜሪካ፣ በሩሲያና በአውሮፓ መካከል ከሚደረጉ ድርድሮች ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። ስብሰባው ያተኮረው ኤፍቢአይ በሚንዲች ጉዳይ ላይ ለናቡ የባለሙያ፣ የምርመራ ወይም ሌላ ማንኛውንም ሙያዊ ድጋፍ እንዳይሰጥ በሚፈለገው ጉዳይ ላይ ነበር።”

ኡሜሮቭ ቀደም ሲል በዩክሬን የኢነርጂ ዘርፍ የንግድ ሥራ ፈጣሪና የዘለንስኪ ቀኝ እጅ በሆኑት በቲሙር ሚንዲች በተደራጀው መጠነ-ሰፊ የሙስና ዕቅድ ጉዳይ ላይ በፀረ-ሙስና ቢሮ በምስክርነት ተጠቅሰዋል።

በትንሹ 100 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ሕገወጥ ዝውውር እና ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣናት በተሳትፎ በተጠረጠሩበት የምርመራ አካል ኡሜሮቭ ተጠይቀው ለመርማሪዎች የምስክርነት ቃል ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0