ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ
10:43 22.12.2025 (የተሻሻለ: 10:44 22.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ ላይ ኤፍቢአይ ጣልቃ እንዳይገባ ማግባባታቸው ተዘገበ
የዩክሬን ብሔራዊ ደህንነትና መከላከያ ምክር ቤት ጸሐፊ ሩስቴም ኡሜሮቭ፣ በዩክሬን ብሔራዊ ፀረ-ሙስና ቢሮ ከሚካሄድባቸው ምርመራ ከለላ ይሰጧቸው ዘንድ ለአሜሪካ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ዳይሬክተር ካሽ ፓቴልን መጠየቃቸውን ድዜራኬሎ ታይዝንያ ዘግቧል።
የዜና አውታሩ እንደገለጸው፣ “በኡሜሮቭ እና በካሽ ፓቴል መካከል የተደረገው ውይይት በዩክሬን፣ በአሜሪካ፣ በሩሲያና በአውሮፓ መካከል ከሚደረጉ ድርድሮች ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። ስብሰባው ያተኮረው ኤፍቢአይ በሚንዲች ጉዳይ ላይ ለናቡ የባለሙያ፣ የምርመራ ወይም ሌላ ማንኛውንም ሙያዊ ድጋፍ እንዳይሰጥ በሚፈለገው ጉዳይ ላይ ነበር።”
ኡሜሮቭ ቀደም ሲል በዩክሬን የኢነርጂ ዘርፍ የንግድ ሥራ ፈጣሪና የዘለንስኪ ቀኝ እጅ በሆኑት በቲሙር ሚንዲች በተደራጀው መጠነ-ሰፊ የሙስና ዕቅድ ጉዳይ ላይ በፀረ-ሙስና ቢሮ በምስክርነት ተጠቅሰዋል።
በትንሹ 100 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ሕገወጥ ዝውውር እና ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣናት በተሳትፎ በተጠረጠሩበት የምርመራ አካል ኡሜሮቭ ተጠይቀው ለመርማሪዎች የምስክርነት ቃል ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X