የኬንያው ፕሬዝዳንት የሉኦ ማኅበረሰብን ቅርስ ለመጠበቅ በዩኔስኮ በተመዘገበው ስፍራ የባሕል ማዕከል ለመገንባት ቃል ገቡ
21:27 21.12.2025 (የተሻሻለ: 21:34 21.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኬንያው ፕሬዝዳንት የሉኦ ማኅበረሰብን ቅርስ ለመጠበቅ በዩኔስኮ በተመዘገበው ስፍራ የባሕል ማዕከል ለመገንባት ቃል ገቡ
ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሚጎሪ ካውንቲ የተካሄደውን 5ኛውን የ"ፒንይ ሉኦ" ፌስቲቫል ለማጠቃለል ባደረጉት ጉብኝት፤ መንግሥት በ"ቲምሊች ኦሂንጋ" ጥንታዊ የታሪክ ስፍራ ላይ በ50 ሚሊዮን የኬንያ ሺሊንግ (በግምት 390 ሺህ ዶላር) ወጪ የባሕል ማዕከል ለመገንባት ማቀዱን የኬንያ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በ16ኛው ክፍለ ዘመን በድንጋይ ግንብ የታጠረ ሰፈራ የነበረውና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበው ይህ ስፍራ፣ የሉኦ ማኅበረሰብን ባሕልና ወግ ለመጠበቅና ለማስተዋወቅ ታስቦ የሚገነባውን አዲሱን ማዕከል ያስተናግዳል።
ሩቶ ይህንን ኢንቨስትመንት በኒያንዛ ክልል እና በመላው ኬንያ የነበሩ የታሪክ የልማት በደሎችን ለማረም የታለመው ተልዕኮ አንዱ አካል መሆኑን መግለጻቸውን ዘገባው ጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X