የሳሕል ጥምረት ጥምር ኃይል በይፋ ተመረቀ፤ ኮንፌዴሬሽኑ 'የማይቀለበስ እውነታ' ነው ሲሉ የማሊ ፕሬዝዳንት ገለጹ
19:27 21.12.2025 (የተሻሻለ: 19:34 21.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሳሕል ጥምረት ጥምር ኃይል በይፋ ተመረቀ፤ ኮንፌዴሬሽኑ 'የማይቀለበስ እውነታ' ነው ሲሉ የማሊ ፕሬዝዳንት ገለጹ
🪖 የማሊ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ባጋራው መግለጫ፣ የሳሕል ሀገራት ጥምረት የተቀናጀ ወታደራዊ ኃይል በብርጋዴር ጄኔራል ዳውዳ ትራኦሬ መሪነት ሥራ ጀምሯል።
አሲሚ ጎይታ በባማኮ በተካሄደው የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት፣ "አዲሱ የጥምረቱ አዛዥ የታጠቁ የሽብር ቡድኖችን አዳዲስ የአሠራር ዘዴዎች አስቀድሞ ከመረዳት ባለፈ፣ የሳሕል ቀጣናን ደህንነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ትግል በበላይነት የመምራትና የመቀጠል ኃላፊነት ይኖርበታል" ብለዋል።
ጎይታ እንደ የሽብር፣ የኢኮኖሚ እና የመረጃ ጥቃቶች ያሉ "በመንግሥታት ከሚደገፉ" ቡድኖች ጥምረቱ ላይ የሚሰነዘሩ ዘርፈ-ብዙ ስጋቶችን ለመከላከል ኮንፌዴሬሽኑ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዷል ሲሉ ተናግረዋል።
እ.ኤ.አ. ከሐምሌ 2024 ጀምሮ የኒጀር፣ የማሊ እና የቡርኪና ፋሶ የጦር ኃይሎች በርካታ የጋራ ዘመቻዎችን ማድረጋቸውንና ይህም "በርካታ የሽብር ቡድን መሪዎችን ለመደምሰስ" ማስቻሉን የማሊው መሪ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ለዚህ ስኬት መገኘት ደግሞ "ጥሩ ዕቅድ፣ ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥ እና ከሁሉም በላይ ጥረቶችን ማቀናጀት" ትልቅ ድርሻ እንዳበረከተ ጠቅሰዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


