የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በኢትዮጵያ ፖሊስ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ልዩ ኮማንዶ አስመረቀ
18:26 21.12.2025 (የተሻሻለ: 18:34 21.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በኢትዮጵያ ፖሊስ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ልዩ ኮማንዶ አስመረቀ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተልዕኮው ልዩና ስትራቴጂያዊ የሆነ "ኤሊት" (ልዩ ኮማንዶ) ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ የትስስር ገፃቸው ላይ አስነብበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም የሚፈታተኑ የሽብርና የከባድ ወንጀል ሙከራዎችን በብቃት የመከላከልና መቆጣጠር ኃላፊነት ተጥሎበታል" ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው ሥልጠናው ማንኛውንም ልዩ “ኦፕሬሽኖች” እና ግዳጆችን በከፍተኛ ብቃት መፈፀም የሚያስችል ጠንካራ አቅም መፍጠሩን ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X





