ከሩሲያ ጋር አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፊታችን ይጠብቀናል - የቱኒዚያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ከሩሲያ ጋር አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፊታችን ይጠብቀናል - የቱኒዚያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

መሐመድ ናፍቲ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት "ባለፈው ዓመት በሶቺ ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር በተገናኘንበት ወቅት፣ ላቭሮቭ የቱኒዚያ-ሩሲያን ግንኙነት ጥንካሬን እና ይህንን ግንኙነት ለማሳደግ ያለውን የጋራ ፍላጎት አረጋግጠዋል" ብለዋል።

በካይሮ ከተካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን መግለጫ የሰጡት ናፍቲ፤ አሁን ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የንግድ፣ የሳይንስ፣ የአካዳሚክ ምርምር እና የቱሪዝም ዘርፎችን እንዲያካትት የማድረግ የጋራ ግብ መኖሩን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል የጋራ ሥራ እንደሚጠበቅ ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።

  የሀገራቱ የጋራ የኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባ እ.ኤ.አ. በ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ውስጥ እንዲካሄድ መርሃ ግብር ተይዞለታል፤ ይህም ለላቀ የሁለትዮሽ የትብብር ምዕራፍ መንገድ ይከፍታል ሲሉ ከፍተኛ ዲፕሎማቱ ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0