የኢትዮ-ሕንድ የድህረ-ምረቃ መርሃ ግብር 1,200 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን የማሠልጠን ዓላማ ሰንቋል
16:43 21.12.2025 (የተሻሻለ: 16:44 21.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮ-ሕንድ የድህረ-ምረቃ መርሃ ግብር 1,200 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን የማሠልጠን ዓላማ ሰንቋል
መርሃ-ግብሩ በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎችና በሕንድ ስመ-ጥር የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ትብብር በአምስት ዓመታት ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደ ነው።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ፣ “በትብብር መርሃ ግብሩ የተካተቱ ስምንት የሕንድ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ችግር ፈቺ የምርምርና ፈጠራ ሥራዎችን በማካሄድ የደቡብ ደቡብ ትብብርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡" ሲሉ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተናግረዋል።
የኢትዮ-ሕንድ የጋራ የድህረ-ምረቃ ትምህርት አስተባባሪ ፕሮፌሰር ክሪሽና ራጅ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ በሰው ሠራሽ አስተውሎትና በቴክኖሎጂ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው ማለታቸውን የአገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያና ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥን የ"ደቡብ-ደቡብ ትብብር" ወሳኝ መገለጫ መሆኑንም ተገልጿል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X