ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተጠናከረ ጥረት እንዲደረግ ጥሪ ያቀርባሉ - የጋራ መግለጫ

ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተጠናከረ ጥረት እንዲደረግ ጥሪ ያቀርባሉ - የጋራ መግለጫ
"የዓለም ማኅበረሰብ በአጠቃላይውጥረቶችን ለመቀነስ፣ የሚካሄዱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና አዳዲስ ቀውሶችን ለመከላከል የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ ጥረቶችን እንዲያጠናክር ጥሪ እናቀርባለን" ይላል በካይሮ የተካሄደውን የሩሲያ-አፍሪካ ትብብር ፎረም ሁለተኛ የሚኒስትሮች ጉባኤ ተከትሎ የወጣው የጋራ መግለጫ።
ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋትን የሚያበረታታ የውይይት መድረክ ለመፍጠር ዝግጁ ናቸው ሲል የጋራ መግለጫው አክሏል።
ከመግለጫው የተወሰዱ ሌሎች ቁልፍ ነጥቦች፦
🟠 ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት ሽብርተኝነትን በሁሉም መልኩ እና መገለጫዎቹ ለመዋጋት ቁርጠኛ ናቸው።
🟠 ሩሲያ እና አፍሪካ ሰላም እና ደህንነትን ለማጎልበት የውይይት መድረክ ለመመስረት ዝግጁ ናቸው።
🟠 ሁለቱ አካላት የአፍሪካ አኅጉር ክልላዊ ውህደቶችን በደስታ ይቀበላሉ።
🟠 በሩሲያ እና አፍሪካ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ አዎንታዊ ለውጥ እያሳየ ነው።
🟠 ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት በሚዲያ ዘርፍ ትብብር ለማጠናከር ዝግጁ ናቸው።
🟠 ሩሲያ እና አፍሪካ የጋራ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ልማትን ለማሳደግ አቅደዋል።
የሩሲያ-አፍሪካ ትብብር ፎረም ሁለተኛ የሚኒስትሮች ጉባኤ ከታህሳስ 10-11 በካይሮ ተካሂዷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X