"የሩሲያ ኩባንያዎች በቦትስዋና ግዙፍ የመሠረተ ልማት ማሻሻያዎች ዙሪያ ስለመሳተፍ ማጤን አለባቸው" - የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

"የሩሲያ ኩባንያዎች በቦትስዋና ግዙፍ የመሠረተ ልማት ማሻሻያዎች ዙሪያ ስለመሳተፍ ማጤን አለባቸው" - የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

"እኛ ክፍት ነን፤ ቦትስዋና ኢንቨስት ለማድረግ ምርጥ ቦታ ናት ብለን በጥብቅ እናምናለን። ማስረጃውም በፖለቲካዊ መረጋጋት የተሻልን እንደሆንን ያሳያል" ሲሉ ፔንዮ ቡታሌ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የሩሲያ አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ በካይሮ ከተካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን፤ በነዳጅ፣ አልማዝ እና ግብርና ዘርፎች የሚያደርጉትን ትብብር ተመልክተዋል። ውይይቱ እነዚህን ዘርፎች የሩሲያን ልምድ በመጠቀም በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና በግብርና መሳሪያዎች ለማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ ነበር።

"በታዳሽ ኃይል ዘርፍ በጋራ የመሥራት ዕድሎችን እንዲሁም በለውጥ የተቀላጠፈ ኢኮኖሚ ለመገንባት በምናቅድባቸው ሌሎች ቁልፍ ዘርፎች ዙሪያ በጋራ ስለመሥራት ተወያይተናል" ሲሉ ቡታሌ ገልጸዋል።

  ጋቦርኔ፤ ስለ አኅጉሪቱ የሚዘግቡ እና የቦትስዋናን የሩሲያ እይታ የሚያንፀባርቁ ቀልጣፋ እና የተማሩ ጋዜጠኞቿ ከስፑትኒክ ጋር እንዲሠሩ እንደምትሻም አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0