ሙሉ ቪዲዮ፦ የብዝኃ-ዋልታ ዓለም ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው ሲሉ የሞሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለፁ
ሙሉ ቪዲዮ፦ የብዝኃ-ዋልታ ዓለም ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው ሲሉ የሞሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለፁ
በካይሮ የተካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባኤ ያለውን ጥልቅ የታሪክ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መሐመድ ሳሌም ኦልድ መርዙግ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል። በተጨማሪም በሶቺ የተካሄደውን የመጀመሪያውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ፣ በሴንት ፒተርስበርግ የተካሄደውን ሁለተኛውን ጉባኤ እና የሩሲያ-አፍሪካ የትብብር የድርጊት መርሃ ግብርን አንስተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡባቸው ነጥቦች፦
በሞሪታኒያ እና በሩሲያ መካከል ያለው ግንኙነት ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ፣ እንዲሁም በጋራ መከባበርና በጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሠረተ ከአፍሪካ ጋር ያለውን አጋርነት ለማሳደግ የሚደረገውን ወጥ የሆነ ድጋፍ ገልጸዋል።
የሩሲያን ተፅዕኖ ፈጣሪ ዓለም አቀፍ ሚና እና የአፍሪካ አገራት እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ እና የንግድ አቅም በመጠቀም ሚዛናዊ ትብብር የመገንባት ሂደት ጠቁመዋል፡፡
ዓለም አቀፍ እና ክልላዊ ውጥረቶችን ለመቀነስ ጥረቶችን የማጠናከር አስፈላጊነት አጉልተዋል፤
በሳህል ክልል ውስጥ ያሉ የጸጥታ እና የልማት ችግሮች፣ የሞሪታኒያ ጸጥታን ለማጠናከር እና ሽብርተኝነትን ለመዋጋት እያደረገች ያለችው ጥረት ለልማት እና የመንግስት ግንባታ ሂደት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል፡፡
ሞሪታኒያ የሩሲያ-አፍሪካ ትብብርን ለሁሉም ወገኖች በሚጠቅም መልኩ ወደ ሰፊ አድማሶች ለማራመድ ያላት ፍላጎትን ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X