ግብፅ በዩክሬን ጉዳይ ላይ ለያዘችው አቋም ሩሲያ አመስጋኝ መሆኗን ሰርጌ ላቭሮቭ ተናገሩ

ሰብስክራይብ

ግብፅ በዩክሬን ጉዳይ ላይ ለያዘችው አቋም ሩሲያ አመስጋኝ መሆኗን ሰርጌ ላቭሮቭ  ተናገሩ

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከካይሮ የሩሲያ-አፍሪካ አጋርነት መድረክ የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ከግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ጋር ተወያይተዋል።

በድርድሩ ወቅት የሚከተሉት ነጥቦች ውይይት ተደርጎባቸዋ፡-

🟠 ዩክሬን ግጭት፡ ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት የመነሻ ምክንያቶቹን ከግምት ውስጥ በማስገባት የመፍታት አስፈላጊነትን በተመለከተ ግብፅ ያላትን ግንዛቤ ዋጋ ጸጣለች ሲሉ የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ገለጸዋል።

🟠 የጋራ ፕሮጀክቶችን ማፋጠን፡ ሩሲያ እና ግብፅ በተለይም በኃይል ዘርፍ፣ ሩሲያ በምትገነባው የኒውክሌር መሠረተ ልማት ላይ ትብብርን ጨምሮ የጋራ ስትራቴጂያዊ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማፋጠን ተስማምተዋል።

የግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ የሆነውና በሩሲያ ከፍተኛ ተሳትፎ እየተገነባ ያለው ኤል ዳባ፣ በኃይል አጋርነታቸው ውስጥ ዋና ፕሮጀክት ሆኖ ቀጥሏል፤ የፋይናንስ መደላድሎችም ከጊዜ ሰሌዳው ጋር እንዲጣጣሙ እየተደረጉ ነው።

🟠 የነገረ-ሶሪያ ቅንጅት፡ ሩሲያ እና ግብፅ የሉዓላዊነትን እና የግዛት አንድነትን የሚያከብር የፖለቲካ ሂደት አስፈላጊነትን አጽናኦት ሰጥተው፣ የሶሪያን አንድነትና መረጋጋት ለመጠበቅ ጥረቶችን ለማስተባበር ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

🟠 የአየር ትስስርን ማስፋፋት፡ በሩሲያ እና በግብፅ መካከል የአየር ትስስርን የማስፋፋት እቅዶችም ተዳስሠዋል፤ ውይይቶቹም የጉዞ ትስስርን ለማሻሻል፣ በተለይም በሩሲያ ከተሞች እና በግብፅ የመዝናኛ ስፍራዎች መካከል፣ ቱሪዝምን እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማሳደግ ላይ ያተኮሩ ነበሩ።

🟠 የእስራኤል-ፍልስጤም ግጭት፡ ግብፅ የፍልስጤምን ጉዳይ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት ሩሲያ ያላትን መርህ ላይ የተመሠረተ አቋም ታደንቃለች። ካይሮ ከጋዛ ጋር በተያያዙ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እና  የትብብር ቁልፍ ዘርፎች ሆነው በቀጠሉ ሰፊ የሰላም ተነሳሽነቶች ውስጥ በንቃት ስትሳተፍ ቆይታለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0