ሩሲያ ለዛምቢያ 2 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የምግብ ዕርዳታ ድጋፍ አደረገች
16:56 19.12.2025 (የተሻሻለ: 17:04 19.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ለዛምቢያ 2 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የምግብ ዕርዳታ ድጋፍ አደረገች
ድጋፉ ዓለም አቀፍ ትብብርን እና የጋራ መከባበር መንፈስን የሚያንፀባርቅ ነው ሲሉ የዛምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ሙታሌ ናሉማንጎ ተናግረዋል።
"የዜጎቻችንን ደህንነት እየጠበቅን የወዳጅነት ትስስርን ማጠናከር እንቀጥል" ሲሉም አክለዋል።
የምግብ ድጋፉ በጎርፍ አደጋ በተጠቁ ቤተሰቦች ላይ የተከሰተውን ረሃብ በእጅጉ እንደሚያቀል የብሔራዊ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ክፍል አስተባባሪ ኖርማን ቺፓኩፓኩ ገልፀዋል።
"የሩሲያ ፌዴሬሽን የምግብ ዋስትና ስጋት የገጠማቸውን ወዳጅ ሀገራት መደገፍ እንደ ግዴታ ይቆጥረዋል" ሲሉ የሩሲያ አምባሳደር አዚም ያራህመዶቭ አብራርተዋል።
ድጋፉ አተር ክክ እና የምግብ ዘይትን እንደሚያካትት አንድ የአካባቢው የዜና ወኪል ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


